Wednesday, September 26, 2012

ዋልድባ ገዳምን ለማፍረስ የተነሳ ሥራው ብቻ ሳይሆን እሱም ይፈርሳል





  • በዋልድባ ዛሬማ ወንዝ ላይ የተሰራውን ድልድይ በመብረቅ ተመ
  • በአቲካ ወንዝ ላይ የተሰራው የሸንኮራ ማልማያ ግድብ  በዚሁ ቀን ፈራርሷል
  • የገዳማውያኑ እንግልት እንደቀጠለ ነው
እግዚአብሔርም ሙሴን ተናገረው፦ ወደ ፈርዖን ግባ እንዲህም በለው። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ያገለግለኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ። ለመልቀቅ እንቢ ብትል ግን እነሆ እኔ አገርህን ሁሉ በጓጕንቸሮች እመታለሁ ፤ ወንዙም ጓጕንቸሮችን ያፈላል፥ ወጥተውም ወደ ቤትህ፥ ወደ መኝታ ቤትህ፥ ወደ አልጋህም፥ ወደ ባሪያዎችህም ቤት፥ በሕዝብህም ላይ፥ ወደ ምድጆችህም፥ ወደ ቡሃቃዎችህም ይገባሉ ፤ ጓጕንቸሮችም በአንተ በሕዝብህም በባሪያዎችም ሁሉ ላይ ይወጣሉ። ኦሪት ዘጸአት 8  ፤ 1-4 አሁንም እግዚአብሔር በዋልድባ ጉዳይ እየተናገረ ይገኛል ፤ ከወራት በፊት በዋልድባ ላይ የተከሰተውን ነገር ሰምቶ ያላዘነ ሰው የለም ፤ በቦታው የሚገኙ መነኮሳትም ከአቅማቸው በላይ ሲሆን “ይግባኝ ለክርስቶስ” ብለው አሳልፈው ሰጥተዋል ፤ መንግስትና በአቋሙ በመጽናቱ እግዚአብሔር ባሳለፍነው ወር አጋማሽ ላይ በሚናገርበት መንገድ ተናግሯል እየተናገረም ይገኛል ፤ አሁንም  በተደረገው ነገር ከመማር ይልቅ እልህ የመጋባት ነገር እየተመለከትን እንገኛለን ፤ ይህ ለማንም አይጠቅምም፡፡

Monday, September 24, 2012

አያት ኦርቶዶክስ ፤ አባት ካቶሊክ ፤ ልጅ ‘ONLY JESUS’


  •  ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ፤ ካቶሊክና ONLY JESUS … በሶስት ትውልድ ሶስት ሃይማኖት!!!!
  •   ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ ደመቀ መኮንን ለክረምት ወደ ቤተሰብ ሲሄዱ እንደ ልጅነታቸው  ቁርዓን በመቅራት እና የአባታቸውን ማሳ በማረስ  ጤፍ ፤ በቆሎና ዳጉሳ በመዝራት አባታቸውን በስራ ያግዙ ነበር፡፡
  •   አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝን ስንተኛ ካዎ እንበላቸው?
  •  Washington DC & # 2176 “SON OF WOLAITA’S KING”
(አንድ አድርገን መስከረም 14 2005 ዓ.ም)፡- ዘወትር ሰዎች ስልጣን ላይ ስላለ ሰው እጅጉን የማወቅ ጉጉት ያድርባቸዋል ፤ አይደለም ጠቅላይ ሚኒስርን የመሰለ ዙፋን ይቅርና ሌላም ስልጣን ቢሆን ብዙ ይባላል ብዙም ይወራል ፤ ስልጣን ላይ የነበረው ሰው ከስልጣን ሲወርድም ምን አይነት ስራ ሲሰራ እንደነበር የማወቅ ጉግታቸው ይጨምራል ፤ እዚህ ግቡ የማይባሉ ሰዎች ወንበሩን ሲይዙት የሁሉም ሰው አይን ውስጥ ይወድቃሉ ፤ ከዚህ  በፊት “ቀይ መብራት” ብለን ባቀረብነው ጽሁፍ ጥቂቶች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር የአቶ ደመቀ መኮንን ሃይማኖት ሙስሊም መሆናቸውን በመጠራጠራቸው ስለ አቶ ደመቀን ጀርባ እንድንጽድላቸው ጠይቀውን ነበር፤  እኛም ጥቂት ካነበብነውና ከቅርብ ሰዎች ከሰማነው መሰረት በማድረግ  ስለ አቶ ደመቀ ፤ ስለ አቶ ኃይለማርያምና መጽሀፍ በማገላበጥ ስለ ወላይታ ጥቂት ማለት እንወዳለን፡፡

Friday, September 21, 2012

ቀይ መብራት



  • ·        አንደኛ ……….. ጠቅላይ ሚኒስትር …….   ONLY JESUS (የሐዋርያ እምነት ተከታይ)
  • ·        ሁለተኛ ……….ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ….. MUSLIM
  • ·        ሶስተኛው …. ጠቅላይ ሚኒስር ለመሆን የታጩት ሰው ….. MUSLIM
(አንድ አድርገን መስከረም 10 2005 ዓ/ም)፡- አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የቀድሞ የውጭ ጉዳይ እና የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ አቶ ደመቀ መኮንን የትምህርት ሚኒስትር ፤ አቶ ሶፊያን አህመድ የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር ፤ እነዚህ  በስም የተዘረዘሩት ሶስት ከፍተኛ የሀገሪቱ ቱባ ባለስልጣናት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በህይወት በተለዩበት ወቅት የኢህአዴግ ፓርቲ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ ለውድድር ያቀረባቸው ሰዎች  ናቸው ፡፡ ፓርቲው ባደረገው ምርጫ መሰረት አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝን ሊቀመንበር ፤አቶ ደመቀ መኮንን ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር አድርጎ መሾሙ የሚታወቅ ነው ፤ በቂ ድምጽ ያላገኙት በወ/ሮ አዜብ መስፍን የተጠቆሙት አቶ ሶፍያን አህመድ በሶስተኝነት ወደ ኃላ ቀርተዋል ፤ ነገ 11/01/2005 ዓ.ም ፓርላማው ምርጫውን በ99.6 በመቶ ድምጽ ያጸድቀዋል ተብሎ ይጠበቃል ፤ አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የOnly Jesus እምነት ተከታይ ናቸው ፤ ምክትላቸው አቶ ደመቀ መኮንንና አቶ ሶፍያ አህመድ ደግሞ የእስልምና እምነት ተከታይ ናቸው ፤ በመሰረቱ ደመቀ መኮንን ብሎ የእስልምና እምነት ተከታይ ይኖራል ብለው ሰዎች ላያስቡ ይችላሉ ፤  አቶ ደመቀም ከወደ ወሎ መሆናቸው ሰዎች ይናገራሉ ፤ አሁን እኛን ያሳሰበን ነገር የኢህአዴግ የፓርቲ ምርጫ አይደለም ፤ የነዚህ ሰዎች ሹመትም አይደለም ፡፡

Tuesday, September 18, 2012

‹‹… ሙሴ በድንጋይ ዘመን የገነነ አንድ እረኛ በመሆኑ ቢሳሳት አይገርምም…›› የበዕውቀቱ ስዩም የዕውርነት ፍሬ


 ቀሲስ  ወንድምስሻ   አየለ 
በዕውቀቱ ስዩም ደፋርና የራሱን የስነጽሑፍ ዘይቤ ለመፍጠር የሚሞክር ገጣሚና ደራሲ መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ፤ ብዙ የሚባሉ የወረቀትና የኤሌክትሮኒክስ ኅትመቶችን አዘጋጅቶ ያበረከተ የታወቀ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ በእንግሊዝኛ የጻፋቸውን ግጥሞች ዋጋ ለክቶ በብልጫው መርጬዋለሁ ያለው ዓለምአቀፍ ድርጅትም በኦሎምፒክ ዋዜማ እንግሊዝ ሀገር ለንደን ወስዶት ግጥሙን አቅርቦና ሌሎችም መርሐግብሮችን አሳትፎ በቴምዝ ወንዝ አካባቢም አዝናንቶትሸኝቶታል፡፡ የሀገራችን የስነጥበብ ባለሙያዎችም ሲሄድ ተሰብስበው ሸኝተውት፣ ሲመጣም ከአቀባበል ጋር ልምዱን ተካፍለውታል፡፡ እንዲህ ነው የሀገር ልጅነት፡፡

Thursday, September 13, 2012

የምህላ ጸሎቱ በአግባቡ እየተካሄደ አይደለም


(አንድ አድርገን መስከረም 3 ፤ 2005 ዓ.ም)፤-ከሳምንት በፊት ቅዱስ ሲኖዶስ ሁለት ሱባኤ ማለትም የ14 ቀናት የጸሎት አዋጅ ማወጁ ይታወቃል ፤ መግለጫው የሚለው ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሁለተናዊ ዕድገት ለሀገሪቱ ሰላምና አንድነት የሚበጅ ተተኪ አባት (ፓትርያርክ) ለቤተ ክርስቲያኗ እግዚአብሔር ባወቀ መርጦ እንዲያስቀምጥ በመላዋ ኢትዮጵያና በውጭ ሀገር በሚገኙት አህጉረ ስብከት፣ ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት ከጳጉሜን 1 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መስከረም 10 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ጸሎተ ምህላ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል የሚል ነው። በአሁኑ ሰዓት አንዳንድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ቤተክርስትያናት ጋር እንዳየነው ከሆነ የቅዱስ ሲኖዶስ የጸሎት አዋጅ በአግባቡ እየተደረገ አለመሆኑን ተመልክተናል ፤ ከአዲስ አበባ ውጪ ባሉ አብያተክርስቲያናት የጸሎት አዋጁ እየተደረገ አለመሆኑን ከተለያዩ ቦታዎች ያገኝናቸው መረጃዎች ያመለክታሉ ፤ ለሀገሪቱ ሰላምና ለቤተክርስትያን የሚበጅ ደግ አባት እግዚአብሔር እንዲሰጠን የጸሎት አዋጅ መታወጁ መልካም ሆኖ ሳለ አዋጁን ግን ከድረ-ገጽ ፤ ከዜና ማሰራጫ ጣቢያዎች በዘለለ በሰፊው በአብያተክርስትያናቱ ቁጥር መመልከት አልቻልንም ፤  በተወሰኑት 14 ቀናት ውስጥ የምህላ ጸሎት ባለመደረጉ ተጠያቂው ማነው? ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያወጣቸውን የተለያዩ መግለጫዎች እና መመሪያዎች ተከታትሎ መከናወናቸውን የሚያረጋግጠው አካል ማነው ? ነገሮች ከወረቀት በዘለለ የሚሰሩትና የሚተገበሩትስ መቼ ነው ?

Monday, September 10, 2012

‹‹ርእሰ ዐውደ ዓመት›› በኢትዮጵያ



ዛሬ ያመቱ፣ 2004 .. 364 ቀን ነው፡፡ ዓመቱ ሊያበቃ፣ ዘመኑ ሊካተት አሮጌ ኾኖ ሊያልፍና አምና የሚለውን ካባ ለመደረብ 24 ሰዓት ወይም 1,440 ደቂቃ ወይም 86,400 ሰከንድ ቀርቶታል፡፡
ርእሰ ዐውደ ዓመት (የዓመት ዙር ዋና መነሻ) በፀሐይ መስከረም 1 ቀን 2005 .. በፀሐይና ጨረቃ ጥምር ኢትዮጵያዊ አቆጣጠር 2013 ዓመት ሊብት ዘመኑም ሊሞሸር፣ ዓመቱም ሊቀመር በናፍቆት እየተጠበቀ ነው፡፡ በባህላዊውና ዓለማዊው ትውፊት ‹‹እንቁጣጣሽ›› በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ‹‹ቅዱስ ዮሐንስ›› እየተባለም ይጠራል፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቷ እያንዳንዱን ዓመት ለአራቱ ወንጌላውያን በመስጠቷ ምእመኖቿና ካህኖቿ የተረኛውን ወንጌላዊ ስም በመጥራት መልካም ምኞታቸውን ይገላለጹበታል፡፡

Friday, September 7, 2012

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስከሬን ያረፈበት 300 ካሬ ሜትር የሚሆን ቦታ ታጠረ





  • “መለስ የራሱ ሀውልት እንዲሰራለት አይፈልግም ፤ የእሱ ምስል ያለበት ሬክላም እንዲሰቀልለትም አይፈልግም”  ወ/ሮ አዜብ መስፍን

 (አንድ አድርገን ጳግሜ 2 2004 ዓ.ም)፡- የጠቅላይ ሚኒስትሩ  ግብዓተ መሬት ከተፈጸመ እነሆ 5 ቀናት አለፉ ፤ አስከሬናቸው ያረፈበት ቦታ ከዚህ በፊት የማንም አስከሬን ያላረፈበት ከቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በስተ ግራ በኩል ይገኛል ፤ በቴሌቪዥን እንደተመለከታችሁት የውስጡ ግድግዳ በሴራሚክ ተነጥፎ ሳጥኑ በክብር አፈር እንዳይበላው ታስቦ አስከሬኑ አርፏል ፤ ሳጥኑ ላይ ወደፊት ሙዚየም እንደሚሰራ ታሳቢ በማድረግ ብዙ ድንጋይ እና አፈር ሊያሸክሟቻ አልወደዱም ፤ ባይሆን ትንሽ ባዞላ ቢጤ ከላይ በማስቀመጥ ክፍተቱን በሲሚንቶ በመሙላት ከላይ የኢትዮጵያ ባንዲራን አልብሰዋቸዋል ፤  

ያለፈው ዘመን ይበቃል ... 1ጴጥ.4፡3

  • የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና። 1ጴጥ.43፡፡ 
  • «ሰውስ ዘመኑ እንደ ሣር ነው እንደ ዱር አበባ እንዲሁ ያብባል፡፡ ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ያልፋል» መዝ.102/103 1516

አባታችን አዳም ጀምሮ ብዙ ትውልድ በዚህች ምድር ላይ ተመላልሷል፡፡ ወጥቷል ወርዷል አልፏል፡፡ ዘመን ሲያልፍ ዘመን ሲተካ ሰው ሲያልፍ ሰው ሲተካ፡ ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ ነቢየ እግዚአሔር ዳዊት በመዝሙሩ«ሰውስ ዘመኑ እንደ ሣር ነው እንደ ዱር አበባ እንዲሁ ያብባል፡፡ ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ያልፋል» መዝ.102/103 1516 ብሏል፡፡ ይህም ቃል በአዳም ልጆች ሁሉ ላይ ሲሠራ ኖሮ ከአሁኑ ትውልድ ደርሷል፡፡ ቋሚ የቆየ የሚመስለው የአሁኑ ዘመን ሰው ግን ሊያስተውለው የሚገባ አንድ ዐቢይ ቁም ነገር አለ፡፡ ይኸውም ከእርሱ በፊት የነበረው ትውልድ ቦታውን ለአሁኑ እንደለቀቀ ሁሉ ይኸኛውም ትውልድ በበኩሉ ኃላፊ መሆኑ ነው፡፡ ታዲያ አሮጊው ዘመን አልፎ አዲሱ ዘመን ሲተካ ክርስቲያኖች አዲሱን ዘመን በምን ዓይነት መንፈስ ነው የምንቀበለው?