Tuesday, July 25, 2017

አንድን መናፍቅ ለማውገዝ ስንት አመት ይበቃል ?


(አንድ አድርገን ሐምሌ 17 2009 ዓ.ም)፡- ባሳለፍናቸው ሁ

ለት አስርት ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በፕሮቴስታንት ጥላ ሥር ለማድረግ በተሐድሶ ምግባር በርካቶች ከውስጥም ሆነ ከውጭ ፤ በቤተክርስቲያኒቱ በተለያዩ የአገልግሎት ማዕረጋት  ያሉ ሰዎችን መከታ በማድረግ መሰረቷን ለመናድ ፤ ቅጥሯን ለማፍረስ ፤ አስተምህሮዋን ለመበረዝ ፤ ቀኖናዋንና ዶግማዋን ለማስረሳት ፤ ካሕናቷን ለማዋረድ ፤ ስሟን የማጠልሸት ፤ ምዕመኗን ከእቅፏ የማስወጣት ሥራ ሲሰራ ነበር ፡፡ ምዕመኑን ከቤተክርስቲያን ቅጥር በማውጣት በአዳራሽ እየሰበሰቡ የ‹‹ወንጌል አገልግሎት›› ሲሰጡም ነበር ፤ በርካታ ሚሊየን ብሮች ከየአዳራሾች በመሰብሰብ የግለሰቦችን ሕይወት በመጠኑም ሲቀይር አይተናል ፤ ብዙዎች አዘቅት ሲወርዱ ጥቂቶች በሀብት ማማ ላይ ሲንሳፈፉም ተመልክተናል ፡፡

Saturday, July 1, 2017

ኑፋቄ የማይሰለቻቸው ቅብጥብጡ ሐራጥቃ

"ኢየሱስ ክርስቶስ ማለት አማላጅም ነው ተማላጅም ነው" ወልደ ትንሣኤ አያልነህ
  

የሰውየን ነገር ከዚህ ቀደም "ጵጵስና" አይገባውም በሚል ሀሳባችንን ለመግለጥ ሞክረናል፡፡ ዲያቆን ኤፍሬም እሸቴ "ኢይደልዎ" በሚል ያቀረበውን ጦማርም ኾነ ሌሎች ብዙዎች ተቆርቋሪዎች ድምጻቸውን ማሰማታቸውን አስታውሳለሁ፡፡ በእነዚያ ምጥን ጦማሮች መነሻነት የተብሰከሰኩ ሁሉ ስሜታቸውን መግለጣቸው ይታወቃል፡፡

እንዲህ ሲለይለት ጥሩ ነውና እዚያም እዚህም ያለነው ቁርጣችንን ዐውቀን መንገዳችን እንዳይንጋደድ ይረዳናል፡፡ ለመወሠንም ጊዜው አሁን ነው፡፡ በውዥንብር የቆዩ ብዙ እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ሰውየው በገባ ወጣ ጨዋታ ስልት የተካኑ ስለነበሩ ብዙዎችን ሲያጭበረብሩ ኖረዋል፡፡ ድሮም ቢኾን በማንኪያ ሲፋጅ ሲበርድ በእጅ እያሉ ሲያምታቱ ቆዩ እንጂ ለማዕዱ ክብር የበቁ አልነበሩም፡፡ ያዳቆነ . . . እንዲሉ የኑፋቄውን ጫፍ እስኪነኩት ድረስ አቻኩሎ እዚህ አደረሳቸው፡፡ ምእመናን በዚህ ሊሸበሩ አይገባም፡፡ በተለይ ዝናን ተከትሎ የሚመጣውን ቅስፈት ማንም አይችለውምና እያሳበደ ከምእመናን በረት አስወጣቸው፡፡ ወደ ውጭ ከማየት ወደ ውስጥ ወደ መመልከት ማዘንበል ያስፈልጋል፡፡ ስለፈቃድ እብደት ሲናገሩ ከራርመው ራሳቸው በፈቃዳቸው አብደው አረፉት፡፡ እግዚአብሔር ይህንን ጽኑ በሽታ ይነቅልላቸው ዘንድ ምኞታችን ቢኾንም ኑፋቄያቸውን ግን አንታገሠውም፡፡